የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ በጄኔቫ/ሴውዘርላንድ ዛሬ በተጀመረው የአለም ንግድ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ (General Council) ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
Back

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ በጄኔቫ/ሴውዘርላንድ ዛሬ በተጀመረው የአለም ንግድ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ (General Council) ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

Motri
5 min read

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ በጄኔቫ/ሴውዘርላንድ ዛሬ በተጀመረው የአለም ንግድ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ (General Council) ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ከጠቅላላ ጉባኤው ጎን ለጎን የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኒጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ እና የኢትዮጵያ የስራ ቡድን ስብሰባ አምባሳደር ሪብቃ ፊሼር ጋር በኢትዮጵያ የድርጅቱ አባልነት ሂደት ላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልፀዋል።

በውይይታችንም በኢትዮጵያ በኩል በባለ-ብዙ እና በሁለትዮሽ የድርድር መድረክ ላይ የተከናወኑ አበይት ተግባራት እና ተግዳሮቶች ላይ የመከርን ሲሆን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ በጠንካራ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እና የቴክኒክ አቅም ላይ እንደምትገኝ እና የድርድር ሂደቱ በፍሬ-ነገርም ጭምር የላቀ መሆኑን ጠቅሼያለሁ ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የድርጅቱን አባልነት ለማሳካት በትኩረት እየሰራች መሆኗን እና ሁለንተናዊ ዝግጁነት እንዳላት ማብራራታቸውን በመጥቀስ ። በተጨማሪም ሂደቱ አሁን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በመድረሱና ድርድሩን ለማጠናቀቅ በሃገራችንም ሆነ በዓለም ንግድ ድርጅት ሴክሬታሪያት በኩል ትኩረት ተሰጥቶት ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸውን ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል ።

የዓለም ንግድ ድርጅ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኒጎዚ ኦኮንጆ እና አምባሳደር ርብቃ ላምፕ በበኩላቸው የኢትዮጵያ አባልነትን በከፍተኛ ትኩረት የሚደግፉ መሆኑን ማረጋገጣቸውንም ገልፀዋል ፡፡

Gallery

Gallery image 1
Gallery image 2
Gallery image 3
Gallery image 4
Gallery image 5

Tags

#Motri#coffee