የሞያሌው ዘመናዊ የቁም እንሰሳት የገበያ ማዕከል ምረቃ
Back

የሞያሌው ዘመናዊ የቁም እንሰሳት የገበያ ማዕከል ምረቃ

Motri
5 min read

የኢፌዴሪ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ይድነቃቸው ወርቁ በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ የሚገነባውን ዘመናዊ የቁም እንሰሳት የግብይት ማዕከል ለማስጀመር ሞያሌ ከተማ ገቡ።

ሚኒስትር ዴኤታው ቦረና ዞን ያቤሉ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በክቡር አቶ አብዱሰላም ዋሪዮ የቦረና ዞን ዋና አስተዳዳሪ የደመቀ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን ከ200 ኪሎ ሜትር የመኪና ጉዞ በኋላ ሞያሌ ከተማ ሲደርሱ በሞያሌ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ገልማ ከሮጲቻ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓቱን ለሁሉም ተዋናይ አካላት ምቹና ዘመናዊ እንዲሁም የምርት ጥራትንና ተወወዳዳሪነትን ለማሳደግ ዘመናዊ የግብይት ማዕከላትንና ሌሎች የገበያ መሠረተ ልማቶችን በማስገንባትና ማስፋፋት ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ይህ በሞያሌ ወረዳ የሚጀመረው ዘመናዊ የቁም እንሰሳት የግብይት ማዕከል የአካባቢውን እምቅ የቁም እንሰሳት ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚያስችል ይታመናል።

Gallery

Gallery image 1
Gallery image 2
Gallery image 3
Gallery image 4
Gallery image 5
Gallery image 6
Gallery image 7
Gallery image 8
Gallery image 9
Gallery image 10
Gallery image 11
Gallery image 12

Tags

#Motri#coffee