ኢትዮጵያ በስምንተኛው የቻይና ዓለም አቀፍ የአስመጪ እና ላኪዎች ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች።
በዚሁ ኤክስፖ ላይ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ የቡና፣ የቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ሀገር በቀል ምርቶች አስመጭና ላኪዎች ምርቶቻቸውንና አገልግሎታቸውን በመያዝ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው በኤክስፖ መክፈቻ ላይ በመገኘት ከቻይናና ከተለያየ የዓለማችን ክፍሎች ከተገኙ አስመጭና ላኪ ድርጅቶች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
ምንጭ: በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ




